


























































Study with the several resources on Docsity
Earn points by helping other students or get them with a premium plan
Prepare for your exams
Study with the several resources on Docsity
Earn points to download
Earn points by helping other students or get them with a premium plan
Database CH-2, Database Concepts, Organization Study to design database
Typology: Schemes and Mind Maps
1 / 66
This page cannot be seen from the preview
Don't miss anything!



























































መጋቢት/2010 ዓ.ም ገ/ኢ/ት/ሚ/ር
የፋይናንስ የህግ ማዕቀፍ ፕሮግራም በጀት
ፊስካል ፖሊሲ
ኤሌክትሮኒክ ግዥ
ኤሌክትሮኒክ ክፍያ
ዘመናዊ ሂሳብ አያያዝና ሪፖርት ዘመናዊ ንብረት አስተዳደር
የውስጥ ቁጥጥር ስርዓት
የፋይናንስ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ
የአቅም ግንባታ
ፋይናንስ ግልፅነትና ተጣቂነት
ማህበራዊ ተጠያቂት
መጋቢት/2010 ዓ.ም ገ/ኢ/ት/ሚ/ር
የፋይናንስ የህግ ማዕቀፍ ፕሮግራም በጀት
ፊስካል ፖሊሲ
ኤሌክትሮኒክ ግዥ
ኤሌክትሮኒክ ክፍያ
ዘመናዊ ሂሳብ አያያዝና ሪፖርት ዘመናዊ ንብረት አስተዳደር
የውስጥ ቁጥጥር ስርዓት
የፋይናንስ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ
የአቅም ግንባታ
ፋይናንስ ግልፅነትና ተጣቂነት
ማህበራዊ ተጠያቂት
“የአገራችንን የመንግሥት ፋይናንስ አስተዳደር ይበልጥ በማሻሻል በስትራቴጂው ዘመን መጨረሻ ላይ ከአፍሪካ የላቀ የፋይናንስ አስተዳደር ስርዓት መሆን ነው”
ሀ. የሚኒስቴሩ ተልዕኮ
“የአገራችንን የመንግሥት ፋይናንስ አስተዳደርን ዘመናዊ፣ ቀልጣፋና ውጤታማ በማድረግ ግልፀኝነትን፣ ተጠያቂነትንና ፍትሃዊነት የሚያሰፍን እና ለኢኮኖሚ ዕድገት አጋዥ እንዲሆን ማድረግ ነው ”
1.2.1. የስትራቴጂው ዋና ዓላማ የስትራቴጂው ዋና ዓላማ የመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር የአገሪቱን የልማት ስትራቴጂ መሰረት ያደረገ ዘመናዊ፣ ቀልጣፋ፣ተጠያቂነት የሰፈነበትና ውጤታማ እንዲሆን ለማስቻል ነው፡፡
1.2.2. የስትራቴጂው ዝርዝር ዓላማዎች ስትራቴጂው የሚከተሉት ዝርዝር ዓላማዎች አሉት፡-
ሀ) ውጤታማ የሆነና በመከከለኛ ጊዜ የልማት ዕቅድ ላይ የተመሰረተ የፕሮግራም በጀት ስርዓት ለማስፈን፣ ለ) የጥሬ ገንዘብ ክፍያና አስተዳደር ስርዓት ለማሻሻል፣
ሐ) የመንግስት ፋይናንስ ሪፖረት አቀራረብ አለማቀፍ ደረጃውን የጠበቀ እንዲሆን በማድረግ
ጥራቱን የጠበቀ፣ የተሟላና ተጠያቂነትን የሚያሰፍን ለውሳኔ ሰጪው አካል የፋይናንስ መረጃን በማቅረብ የውስጥ ቁጥጥር ስርዓቱን ለማጠናከር፣
መ) የተቀናጀ የመንግሥት ፋይናንስ አስተዳደር የመረጃ ሥርዓት (IFMIS) የመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር የምዝገባ ስርዓት እንዲሆን ለማስቻል፣ ሠ) የመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር መረጃዎች ለዜጎች ተደራሽን እንዲሆኑ በማድረግ ግልጽነትን፣ ተጠያቂነትንና አሳታፊነትን ለማስፈን፣
ረ) የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር በዘመናዊ ስርዓት እንዲመራ ለማድረግ ፣ ሰ) በመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር ተግባራት ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎች የሙያ ደረጃ እና ብቃት ለማሳደግ፣
ሸ) የመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር የማሻሻያ ስራዎች ስርዓተ ፆታን እና ልዩ ልዩ ፍላጎት ያላቸውን የማህበረሰብ ክፍሎች አሳታፊነት እና ተጠቃሚነት ማሳደግ፣ ነው፡፡
የመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር በተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና ሃገሮች የተለያየ ትርጓሜ የተሰጠው ሲሆን በዚህ ስትራቴጂ የመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር ማለት የፊሲካል ፖሊሲን፣ በጀት አስተዳደርን፣ የጥሬ ገንዘብ ክፍያና አስተዳደርን፣ የብድር አስተዳደርን፣ የሂሳብ አያያዝና ሪፖርትን አቀራረብን፣የኦዲትና የውስጥ ቁጥጥርን፣ የግዥና ንብረት አስተዳደርን እና ሌሎች ተያያዥ የክትትል ስራዎች ማለት ነው፡፡
ይህ ስትራቴጂ የሚተገበረው ከ2010 እስከ 2014 በጀት ዓመት ሲሆን የትግበራ መስኮቹ የፊሲካል ፖሊሲ፣ ታክስ ፖሊሲ፣ የፕሮግራም በጀት፣ የጥሬ ገንዘብ ዝግጅትና የክፍያ አስተዳደር፣ የብድር አስተዳደር፣ የመንግስት የሂሳብ አያያዝና ሪፖርት አቀራረብ፣ የውስጥ ኦዲትና ቁጥጥር፣ የግዥ እና ንብረት አስተዳደር፣ የመረጃና የክትትል ስርዓት እና የመንግስትና የግል አጋርነት ያጠቃልላል፡፡
ከ1983 በጀት ዓመት በፊት የአገራችን የመንግሥት ፋይናንስ አስተዳደር የተሟላ የሕግ ማዕቀፍ ስላልነበረው ፋይናንሱን በማስተዳደርና በመቆጣጠር በኩል ከፍተኛ ችግሮችና ክፍተቶች ነበሩበት፡፡ በዚህም ምክንያት የተነሳ በ1987 በጀት ዓመት የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ከፍተኛ
ከላይ የተዘረዘሩትን የጥናቱን ውጤቶች መሠረት በማድረግ በአገሪቱ የሚገኘውን የሲቪል ሰርቪስ ሚናና አወቃቀር በአዲስ መልክ ማሻሻል ተገቢ ሆኖ በመገኘቱ የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ሪፎርም ፕሮግራም ከሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም አምስቱ ንዑሳን ፕሮግራሞች አንዱ ሆኖ እንዲቀረጽ ተደረጓል፡፡ የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ማሻሻያ ሪፎርምም ዓላማዎችና ግቦችን ተቀርጾለት እና በተለያዩ ፕሮጀክቶች በማደራጀት የማሻሻያው ስራዎች እንዲሰሩ ተደርጓል፡፡
የወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ማሻሻያ ፕሮግራም የመንግሥት ፋይናንስ አስተዳደርን ውጤታማ ለማድረግና፣ ግልፅነትና ተጠያቂነትን ለማስፈን የተለያዩ 12 ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ ስራ ላይ አውሏል፡፡
ፕሮጀክቶቹም የመንግሥት ፋይናንስ የህግ ማዕቀፍ ማሻሻያ፣የበጀት አስተዳደር ማሻሻያ፣ የመንግሥት ወጪ ዕቅድ ማሻሻያ፣ የጥሬ ገንዘብ አስተዳደርና ክፍያ አሠራር ማሻሻያ፣ የመንግሥት ሂሣብ ማሻሻያ፣ የውስጥ ኦዲት ማሻሻያ፣ የተቀናጀ የፋይናንስ መረጃ ሥርዓት ማሻሻያ፣ የመንግሥት ግዥ ሥርዓት ማሻሻያ፣ የመንግሥት ንብረት አስተዳደር ማሻሻያ፣ የሂሣብና ኦዲት ሙያ ማሻሻያ፣ የፋይናንስ ግልጽነትና ተጠያቂነት እና የውጪ ኦዲት ማሻሻያ ሲሆኑ ከእነዚህ የማሻሻያ ፕሮጀክቶች መካከል የመጀመሪያዎቹ አስራ አንዱ በማሻሻያ ፕሮግራሙ የቅርብ ክትትል የሚደረግባቸው ሲሆን፣ ያስገኙት ውጤቶች በሚቀጥለው ምዕራፍ በዝርዝር ቀርቧል፡፡
የመንግሥት ፋይናንስ አስተዳደር ቀልጣፋና ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመምራት ሁለት አዋጆች የወጡ ሲሆን እነሱም የፌዴራል መንግሥት የፋይናንስ አስተዳደር እና የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር አዋጆች ናቸው፡፡ እነዚህን አዋጆች ተከትለው የመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር ደንብ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸድቋል፡፡ አዋጆቹንና የፋይናንስ ደንቡን ለማስፈጸምና የበለጠ ለማብራራት ብዛታቸው 16 ያህል የመንግሥት የፋይናንስ፣ ግዥና ንብረት አስተዳደር መመሪያዎች ወጥተዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በአዋጆቹ፣ ደንብ እና የአፈፃፀም መመሪያዎች የተገለጹትን ዋና ዋና ተግባራትን ሂደትና ዝርዝር አፈጻጸም የሚያመለክት እና ሠራተኞችን/ፈጻሚዎችን ቅልጥፍና እንዲጨምር ሊያግዝ የሚችል የአሠራር ማንዋሎች ተዘጋጅቷል፡፡
እነዚህም ማንዋሎች የፕሮግራም በጀት፣ የጥሬ ገንዘብ አስተዳደርና የክፍያ አሠራር፣ የሂሣብ አያያዝ ሥርዓት፣ የውስጥ ኦዲት፣ የክዋኔ ኦዲት፣ የመንግሥት ግዥ አፈፃፀም፣ የመንግሥት ቋሚ ንብረት አስተዳደር፣ የስቶክ ማኔጅመንና የፋይናንስ ግልጽነትና ተጠያቂነት ያጠቃልላል፡፡ ይህም የአገራችን የመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር በተሟላ የህግ ማዕቀፍና ተቋማዊ አሰራር እንዲመራ አስችሏል፡፡
የመንግስት ገቢን ለማሻሻል በርካታ የማሻሻያ ተግባሮች የተከናውነው ሲሆን ዋና ዋናዎቹ፡-
በወጪ ዕቅድ ፕሮጀክት ስር የመንግሥት ኢንቨስትመንትና የመንግሥት ወጪ ፕሮግራሞች የነበሩ ሲሆን ዓላማውም በፖሊሲዎች፣ በዕቅድና በበጀት መካከል ሊኖር የሚገባውን ቅንጅት ለማሻሻል የተቀረጸ ነበር፡፡ በዚሁ መሰረትም የወጪ ዕቅድን ለማሻሻል በተሰሩ ሥራዎች የሚከተሉት ዋና ዋና ውጤቶች ተገኝተዋል፡-
መንግስት የሂሳብ አያያዝ የማሻሻያ የተገኙ ዋና ዋና ውጤቶች፡-
በመንግሥት ግዥ እና ንብረት ማሻሻያ የተገኙ ዋና ዋና ውጤቶች፡-
በውስጥ ኦዲት መሻሻያ የተገኙ ዋና ዋና ውጤቶች፡-
እና የግሉ ዘርፍ ለኢኮኖሚ ዕድገት ያላቸውን ወሳኝነት የማበላለጥ ወይም ለአንዱ ቅድሚያ የመስጠት አዝማሚያዎች የተከሰቱ ቢሆንም በአጭር ጊዜ ከድህነት ተላቀው ብልፅግናን የተላበሱ አገሮች ተሞክሮ የሚያሳየው የመንግሥትን ሚና ወሳኝ መሆኑን ነው፡፡ በመሰረቱ ማንኛውም ለልማት የቆመ መንግስት ሁሉ ልማታዊ መንግስት ነው ማለት ይቻላል፡፡ ሆኖም በኢኮኖሚ ልማት ንድፈ ሃሳብ ልማታዊ መንግስት በመባል የሚታወቁት የምስራቅ ኤሽያ አገሮች በተለይም የኮሪያና የታይዋን መንግስታት ዓይነት የልማት አቅጣጫ የሚከተሉት ሲሆኑ፣ ይህ የልማታዊ መንግስት ኢኮኖሚ ሞዴል እነዚህ አገራትን በአጭር ጊዜ ውስጥ ከድህነት ተላቀው በኢኮኖሚያቸው የበለጸጉ አገራትን እንዲቀላቀሉ አስችሏቸዋል፡፡ ለዚህ ውጤት ደግሞ መንግስታት በኢኮኖሚው እንቅስቃሴ ውስጥ የነበራቸው ሚና የጎላ ነበር፡፡ በአጠቃላይ ሲታይ ልማታዊ መንግስታት በ ዋና ባህሪት ከሌሎቹ ይለያሉ፡፡ እነዚህም በመጀመሪያ ልማትን የህልውናቸው ጥያቄ ያደረጉ መንግስታት በመሆናቸው ከድህነት ለመውጣት ብርቱ ትግል ያደርጋሉ፤ በሁለተኛነት መንግስት ባለሃብቱን በሙሉ ልብ የመደገፉ መርህ እንደተጠበቀ ሆኖ ከባለሃብቱ ፖለቲካና አስተሳሰብ ተጽዕኖ ነፃ በመሆን የሚንቀሳቀስ ሲሆን፣ በሶስተኝነት ደግሞ ልማታዊ መንገዱ ለተከታታይ ዓመታት ቀጣነት እንዲኖረው ልማታዊነት የአስተሳሰብ የበላይነቱን ያረጋገጠበት ሥርዓት እንዲሆን ያደርጋሉ፡፡
በአገራችንም ከላይ የተዘረዘሩትን ሦስት የልማታዊ መንግስት ባህሪያት በመያዝ እና በተጨማሪም በአራተኛነት ዲሞክራሲን በአገሪቱ ማስፈን የሞት ሽረት ጉዳይ አድርጎ በመውሰድ እንዲሁም በአምስተኛነት የህዝብ ተሳትፎና ባለቤትነትን የልማታዊ መንግስቱ ባህሪያት አድርጎ በመውሰድ መንግስት የልማታዊ መንግስት ኢኮኖሚ ሞዴል መከተል ከድህነትና ከኋላ ቀርነት በማላቀቅ አገሪቱን በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ መካከለኛ እና በሂደትም ወደ በለፀገ ኢኮኖሚ ሊያሸጋግር እንደሚችል በመረዳት ከአገሪቱ ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ስርዓቱን በተለይ ከ1994 ዓ.ም. ጀምሮ በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡ በልማታዊ መንግስት ስርዓት መንግስት በኢኮኖሚው ውስጥ ያለው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ፣ በመንግስት በኩል ከፍተኛ የሆነ ሀብት ወጪ ተድርጎ ኢኮኖሚውን የማንቀሳቀስ፣ የገበያ ክፍተት ባለበት ክፍተቱን የመሸፈን ተግባር ይከናወናል፡፡ ይህም ውሱን የሆነውን የመንግስት ሀብት በቁጠባና በብቃት ማስተዳደርና ጥቅም ላይ ማዋልን የሚጠይቅ ይሆናል፡፡ ለዚህም የመንግስትንም ሆነ የግሉን ዘርፍ የማስፈጸም አቅም መገንባት እና የፋይናንስ አቅም በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግን ይጠይቃል፡፡ ለዚህም ባለፉት ተከታታይ 15 ዓመታት ድህነት ተኮር ለሆኑት የመሰረታዊ አገልግሎቶችና እና የመሰረተ ልማት ፕሮግራሞች መንግስት ከፍተኛ በጀት በመመደብ፣ የገበያ ክፍተት ባለበት ላይ በቀጥታ ጣልቃ በመግባት፣ የግሉን ዘርፍ ለማበረታታት የሙያ ድጋፍ በመስጠት፣ ብድር በማመቻቸት፣ የግብር እፎይታን ጨምሮ ለሚያካሂዷቸው ኢንቨስትመንቶች የቀረጥ ነፃ መብት ተጠቃሚ እንዲሆኑ በማድረግ ዘርፍን የመደገፍ ስራ ተሰርቷል፡፡
ለዚህም በአገራችን በተለይ ባለፉት 15 ዓመታት በሁሉም ዘርፍ መጠነ ሰፊ የአቅም ግንባታ ማሻሻያ ፕሮግራሞች ተነድፈው በመተግበራቸው የአገሪቱ የማስፈጸም አቅም በከፍተኛ ደረጃ
ተሻሽሏል፡፡ ለዚህም በተለይ በትምህርት፣ በጤና፣ በመንገድና በመጠጥ ውሃ ተደራሽነትና ሽፋን፤ በኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት፣ በግብርና ምርት ዕድገት፣ በኢንዲስትሪ መስፋፋት ወዘተ የተገኙት ዕድገቶች በአመዛኙ መንግስት በቅድሚያ ተነሳሽነት ያከናወናቸው ናቸው፡፡ ይህም በመሆኑ ባለፉት ተከታታይ አስር ዓመታት የአገሪቱ ኢኮኖሚ ከአስር በመቶ በላይ በማደግ ከዓለም ቀዳሚ የኢኮኖሚ ዕድገት ከተመዘገበባቸው ጥቂት አገራት አንዷ ለመሆን ከመብቃታችን በተጨማሪ የህዝባችን የድህነት ምጣኔ ከግማሽ በላይ ቀንሷል፡፡
የመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር ሥርዓቱን በማሻሻል የማስፈጸም አቅሙን ለመገንባት በተሰሩ ስራዎችም በፌዴራልና በብሄራዊ መንግስታት እስከ ታችኛው የአስተዳደር እርከን ድረስ መጠነ ሰፊ የፋይናንስ ህግና የአሰራር ስርዓት ማሻሻዎች የተደረጉ ሲሆን፣ በዚህም የመንግስት ወጪ አስተዳደሩ በዘመናዊና ቀልጣፋ ከመሆኑም በተጨማሪ የመንግስት ገቢን በከፍተኛ መጠን ሊያድግ ችሏል፡፡ በተለይም ከ1994 በፊት በተካሄዱ የመንግሥት ገቢ ማሻሻያ እርምጃዎች የወራሽነት ባህሪ የነበራቸውን የታክስ ማስከፈያ መጣኔዎች ዝቅ በማድረግ፣ የታክስ መሠረቱን በማስፋትና አስተዳደሩን በማሻሻል እንዲሁም ያልተማከለ የመንግሥት ፋይናንስ አስተዳደር ዕውን በማድረግ የሀገር ውስጥ ገቢን ለማጐልበት ጥረት ተደርጓል፡፡ ሆኖም የተወሰዱት እርምጃዎች የሚፈለገውን የፋይናንስ አቅም ማመንጨት ባለመቻላቸው ተጨማሪና የተጠናከሩ የገቢ ፖሊሲና አስተዳደራዊ ማሻሻያዎችን ማድረግ ግዴታ ሆኗል፡፡
ታክስ የመንግሥት ዋናው የገቢ ምንጭ በመሆኑ ለውጤታማነቱ መሥራት ግዴታ ነው፡፡ የታክስ ፖሊሲው ተፈላጊውን ገቢ ከማመንጨት ባሻገር ሌሎች ዓላማዎችን ለማስፈፀም መዋል ይኖርበታል፡፡ መንግሥት የታክስ ፖሊሲው የዜጐችን የመሥራት ፍላጐት ለማበረታታት፣ የገቢ ልዩነት ለማጥበብ፣ የኢንቨስትመንትን አቅጣጫ ለመምራት፣ እንዲሁም ያልተፈለጉ ምርትና አገልግሎቶችን ለመቆጣጠር ይገለገልበታል፡፡ በአገራችንም ሥራ ላይ የዋሉ የታክስ ፖሊሲዎች በዋናነት ገቢን ለማሳደግ ትኩረት ያደረጉ ቢሆንም እነዚህን ተጓዳኝ የፖሊሲ መሣሪያዎች ተግባራዊ ለማድረግ ረድተዋል፡፡ በሌላም በኩል የታክስ ፖሊሲው የታክስ አስተዳደሩ ውጤታማ፣ የማያዳላና አስተዳደራዊ ብቃትን የሚያጐለብት እንዲሆን የማድረግ ሥራ ተከናውኗል፡፡ እነዚህንም የታክስ ፖሊሲ ዓላማና መርሆዎች ተግባራዊ ለማድረግ የተከናወኑ የታክስ ፖሊሲ ማሻሻያ እርምጃዎች የሚከተሉትን መሠረት ያደረጉ ናቸው፡፡ እነዚህም፡-
ባለፉት በርካታ ዓመታት ሥራ ላይ የዋለው የፊሲካል ፖሊሲ የመንግሥት ገቢ ለማሳደግ ትኩረት ከመሰጠቱም ባሻገር የተሰበሰበው ገቢ የመንግሥትን ኃላፊነት ለመወጣት በሚያስችሉ ልማትን ለማፋጠንና፣ ድህነትን ለመቀነስና መሠረታዊ አገልግሎቶችን ለማቅረብ በሚረዱ የወጪ ዘርፎች የተመደበና አስተዳደሩም ውጤታማ እንዲሆን በርካታ የማሻሻያ እርምጃዎች ተቀርጸው ተግባራዊ ሆነዋል፡፡
ከ1984-1993 በነበሩት 10 ዓመታት የሽግግሩ ወቅት መንግሥት ሆነ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ መንግሥት አገሪቱን ከድህነት ለማውጣት የሚያስችል መሠታዊ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራሞች ተነድፈዋል፡፡ ፕሮግራሞቹን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችሉ እስትራቴጂዎችና ስልቶች የተዘረጉ ሲሆን ዋና ዋና የኢኮኖሚና ማህበራዊ ክፍላተ ኢኮኖሚዎች የሚመሩበት ፕሮግራሞችንም ሥራ ላይ ውለዋል፡፡ ሆኖም እነዚህ እንቅስቃሴዎች ፈጣንና ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚና ማህበራዊ ለውጦችን ማምጣት ባለመቻላቸው መንግስት በ ዓ.ም ወዲህ የኢኮኖሚ ፖሊሲውን በማሻሻልከድህነት በአጭር ጊዜ ለመላቀቅና የኢኮኖሚ ልማትን ለማፋጠን የልማታዊ መንግስት ሞዴል ተመራጭ ሆኗል፡፡የኢኮኖሚ ፖሊሲን ከልማታዊ መንግስት ሞዴል ጋር በማጣጣም ልዩ ልዩ የክፍላተ ኢኮኖሚ ፖሊሲ፣ እስትራቴጂና ስልቶችን በመንደፍ ተግባራዊ ሆነዋል፡፡ ከእነዚህ መካከል ሚከተሉት በዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡ እነዚህም፡-
በእነዚህ የመንግሥት ፖሊሲ፣ እስትራቴጂና ፕሮግራሞች ላይ መሠረታዊ ጽሁፎች እንዲዘጋጁ፣ ለዜጐች እንዲሠራጩና በውይይት እንዲዳብሩ ተደርጓል፡፡ ይህም አካሄድ በአገሪቱ የልማት እስትራቴጂ ስልትና አፈጻጸም ላይ አስፈጻሚ አካላትና ህዝቡ በቂ ዕውቀትና ግንዛቤ እንዲኖራቸው እንዲሁም አገራዊ የጋራ አመለካከትና እምነት እንዲኖር ለማድረግ ረድቷል፡፡ እነዚህን መሠረታዊ የመንግሥት ፖሊሲና እስትራቴጂዎች መሠረት በማድረግ ከ1995 ጀምሮ ተከታታይነት ያላቸው የድህነት ቅነሳ ፕሮግራሞች ሥራ ላይ ውለዋል፡፡ የመጀመሪያው የዘላቂ ልማትና የድህነት ቅነሳ ፕሮግራም (SDPRP) ከ1995-1997 ተግባራዊ የተደረገ ሲሆን፣ በቀጣይም በዚህ ፕሮግራም የአፈጻጸም ግምገማ ላይ በመንተራስ ከ1998-2002 የቆየ ሁለተኛው ፈጣንና
ቀጣይነት ያለው ልማት በማስፈን ድህነትን በሂደት ማስወገድ ዓላማው ያደረገ (PASDEP) የልማት ዕቅድ ተዘጋጅቷል፡፡ በአሁኑ ወቅት በመተግበር ላይ ያሉት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዶች፤ (GTP) ከ2003-2007፣ እንዲሁም (GTP) IIከ2008-2012 በመካሄድ ላይ ይካሄዳል፡፡
የተጠቀሱት የልማትና ድህነት ቅነሣ ብሎም አገሪቱን ከድህነት ለማላቀቅ እንደሚረዱ የታመነባቸው ፕሮግራሞች ከቀበሌ እስከ አገር አቀፍህ ህብረተሰቡን እንዲሁም የአገሪቱን የልማት አጋሮች በማሳተፍ የተዘጋጁ ናቸው፡፡ እያንዳንዱ የልማት ዕቅድም አገራዊና ዓለም አቀፍ ነባራዊ ሁኔታዎችን እንዲሁም ወቅታዊ የአገሪቱን ሁኔታ በማገናዘብ የየራሳቸውን መሠረታዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ያስቀምጣሉ፡፡ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዶች ፈጣን ዕድገትን ከማስገኘት ባሻገር በሁሉም ዘርፎች የተሻለ ውጤትን በማስመዝገብ አገሪቱን ከድህነት በማላቀቅ በሚቀጥሉት 10-15 ዓመታት ወደ መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገሮች ለማሰለፍ የሚያስችሉ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ዕድገት መሠረቶችን ለመገንባት ዓላማ ያደረጉ የልማት ምሶሶዎችን ቀምሯል፡፡ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በሚል ርዕስ የተዘጋጀው የ5 ዓመቱ የልማት ዕቅድ ዓበይት ዓላማዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡ እነዚህም፡-
እነዚህን ዓላማዎች በማሳካት ፈጣን፣ ቀጣይና ሁሉን አቀፍ የሆነ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣት የሚያስችሉ እስትራቴጂዎች በዕቅዱ ተካተዋል፡፡ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድም ሆነ ያለፉት የዘላቂ ልማትና ድህነት ቅነሣ ፕሮግራሞች አመርቂ ውጤት ማሳየታቸውን በየጊዜው የተደረጉ የአፈጻጸም ግምገማዎችና ሪፓርቶች አሳይተዋል፡፡
አገራችን ዘርፈ ብዙ የልማት እንቅስቃሴ በማድረግ የዜጐችን የኢኮኖሚና ማህበራዊ ህይወት ለማሻሻል በድህነት ላይ ጦርነት መክፈቷ ይታወቃል፡፡ ለዚህ ዓላማ መሳካትም መንግሥት አግባብ ያለው ፖሊሲን ከመቅረፅና ለግሉ ክፍለ ኢኮኖሚ አመች ሁኔታን ከመፍጠር ባሻገር ድህነት ተኮር